|
እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ (፫) በእንተ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ (፫) ኪርያላይሶን (፫)
ኦ....! አምላክ (፫)
ያድነን እመአቱ ይሰውረነ በምህረቱ (፫)
|
እንደ ቸርነትህ አቤቱ ማረን (፪)
|
|
የዘወትር ጸሎት ውዳሴ ማርያም
በጌታዬ
በኢየሱስ
ክርስቶስ
ትዕምርተ
መስቀል
ፊቴንና
መላ
ሰውነቴን
ሶስት
ጊዜ
አማትባለሁ።
ሁሉን የፈጠረ አንድ አምላክ በሚሆን በእግዚአብሔር አብ እናምናለን። ሰማይና ምድርን የሚታየውንና የማይታየውን የፈጠረ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን። ዓለም ሳይፈጠር ከርሱ ጋር በነበረ የአብ አንድ ልጅ በሚሆን በአንድ ጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እናምናለን። ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ አምላክ የተፈጠረ ያይደለ የተወለደ በመለኮቱ ከአብ ጋር የሚተካከል ሁሉ በእርሱ የሆነ ያለ እርሱ ግን ምንም ምን የሆነ የለም በሰማይም ካለው በምድርም ካለው ስለኛ ስለ ሰዎች ስለ መዳናችን ከሰማይ ወረደ በመንፈስ ቅዱስ ግብር የተነሳ ከቅድስት ድንግል ማርያም ፍጽሞ ሰው ሆነ፣ ሰው ሆኖ በጴንጤናዊ በጲላጦስ ዘመን ስለ እኛ መከራን ተቀበለ፣ ታመመ ሞተ ተቀበረ በሶስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሳ በቅዱሳት መጻሕፍት እንደተጻፈ በክብር በምስጋና ወደ ሠማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ ዳግመኛም በሕያዋንና በሙታን ይፈርድ ዘንድ በምስጋና ይመጣል። ለመንግሥቱም ፍፃሜ የለውም። ጌታ ማሕየዊ በሚሆን ከአብ በሰረጸ በመንፈስ ቅዱስ እናምናለን እንሰግድለታለን እናመሰግነዋለን፣ ከአብና ከወልድ ጋራ በነቢያት የተናገረ ነው። ከሁሉም በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሰርዋት በአንዲት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን። ኃጢያት በሚሰረይባት በአንዲት ጥምቀት እናምናለን የሙታንንም መነሳት ተስፋ እናደርጋለን የሚመጣውንም ሕይወት ለዘላለሙ አሜን፣
ይዌድስዋ መላእክት
በ 6ኛው ወር ገብርኤል መልአክ ከእግዚአብሔር አብ ዘንድ ተላክ ካንዲት አገር ናዝሬት ገሊላ ከምትባል ለዮሴፍ እጮኛ ከሆነች ከድንግል ዘንድ። የዚች የድንግል ስሟ ማርያም ነው መልአኩ ወደ እርስዋ ገብቶ እንዲህ አላት ደስታ ይገባሻል እግዚአብሔር ከሥጋሽ ሥጋ ከነፍስሽ ነፍስ ነሥቶ ካንቺ ሰው ሆኗልና ከሴቶች ይልቅ አንቺ ብርክት ነሽ ...ከቃሉ አነጋገር አይታ ደነገጠች እንዲህም አለች እንዲህ ያለ የምስጋና እጅ መንሻ ይደረግልኛል? መልአክ እንዲህ አላት ማርያም ሆይ አትፍሪ ከእግዚአብሔር ዘንድ ባለሟልነትን አገኝተሻልና እነሆ ትፅንሻለን ትወልጃልሽ ስሙንም ኢየሱስ ትይዋለሽ እርሱም ታላቅ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል እግዚአብሔር አምላክም የዳዊት ያባቱን ዙፋን ይሰጠዋል እርሱም በያዕቆብ ወገን ለዘላለሙ ይነግሳል መንግስቱም አያልፍም፤ ማርያምም መልአኩን እንዲህ አለችው ይህ ነገር እንደምን ይሆንልኛል እንዘ ኢየአምር ብእሴ መልአኩም እንዲህ አላት፤ መንፈስ ቅዱስ ይጠብቅሻል የሉዑል ኃይሉም ያድርብሻል ይህ የሚወልደው ከሦስቱ ቅዱስ አንዱ ቅዱስ ነው እነሆ ኤልሣቤጥ ካንቺ ወገን የምትሆን ከሸመገለች ካረጀች በኋላ ፀንሰች ልጅም አገኘች እነሆ ይህ ስድስት ወር ሆነ መካን ሲሏት ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና ማርያምም መልአኩን እንደ ቃልህ ይደረግልኝ እኔ ለእግዚአብሔር ባሪያው ነኝ አለቸው።
መልአኩ ገብርኤል ማርያም ድንግል ላንቺ ክብር ምስጋና ይገባሻል አላት። ወላዲተ አምላክ ምስጋና ይገባሻል ቅድስት ነሽና ምስጋና ይገባሻል የመለኮት ምደሪያ ነሽና ምስጋና ይገባሻል የተሸለምሽ ድንኳን ነሽና ምስጋና ይገባሻል የመላእክት እኅት የሕዝቡ ሁሉ እናት ነሽና ምስጋና ይገባሻል የሁሉ እመቤት ማርያም ምስጋና ይጋባሻል የሁሉ ፍቅረኛ ማርያም ምስጋና ይገባሻል ልዑል ማደሪያው ትሆኝ ዘንድ መርጦሻልና ምስጋና ይገባሻል በወርቅ የተሸለምሽ የርግብ ክንፍ በብር ያጌጥሽ ምስጋና ይገባሻል ጎኖችሽ በወርቅ አመልማሎ የተሸለሙ ላንቺ ምስጋና ይገባሻል። የምሥራቅ ደጃፍ የብርሃን እናቱ ላንቺ ምስጋና ይገባሻል ከፀሐይ ሰባት እጅ የምታበሪ ክብርሽ ከአድባራቱ ሁሉ ከፍ ከፍ ያለ አንቺ ምስጋና ይገባሻል ከፀሐይ ሰባት እጅ የምታበሪ ክብርሽ ከአድባራቱ ሁሉ ከፍ ከፍ ያለ ላንቺ ምስጋና ይገባሻል። ማርያም ሆይ ከተመረጡ የተመረጥሽ ከተከበሩ ላንቺ ምስጋና ይገባሻል ከጌታችን ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ለምኝልን ያድነን ዘንድ ከአባቱ ምስጋና ከስቅዱሳን መላእክቶቹ ጋር በመጣ ጊዜ ጻድቅንን በቀኙ ኃጥአንን በግራው ባቆመ ጊዜ እኛን ከሰማዕት እንጢፋኖስ ከመጥምኩ ዮሐንስ ጋር ከሁሉ ቅዱሳን ከሰማዕታት ጋር ያቆመን ዘንድ ለምኝልን ለዓለመ ዓለም ለዘለዓለሙ ይቅር ይበለን። |